አድናቆት
ስለእራሱ ጥሩ ነገር እየተነገረው ያደገ ልጅ ማድነቅን ይማራል
አግባብነት ያለው ማበረታቻ እያገኘ ያደግ ልጅ በእራስ መተማመንን ይማራል
መቻቻል በሰፈነበት ሁኔታ ያደገ ልጅ ትዕግስተኝነትን ይማራል
ልጅ ከአድሎ ነጻ በሆነ ሁኔታ በአግባቡ ካደገ ፍትህን ይማራል
ልጅ ዋስትናና ደህንነት በተመላበት ኑሮ ካደገ ሰውን ማመንን ይማራል
ልጅን በማንነቱ ተቀብለን በማቅረብ ካሳደግነው ምሉዕ ፍቅር ከአለም ይማራል
ጥላቻ በተመላበት አካባቢ ያደገ ልጅ ጠባጫሪነትን ይማራል
ልጅ በሃፍረት ካደገ የጥፋተኝነት መንፈስን ይማራል
…. እንዳለው ዶርቲ ሎው
በየትኛውም ስፍራ የሚኖር የሰው ልጅ ህጻንም ይሁን አዋቂ አድናቆትንና ሙገሳን ይወዳል እንዲሁም ይፈልጋል፡፡ መደነቅ በሰዎች ዘንድ ትኩረት ማግኘታቸንን ስለሚያመላክት ተደናቂው ክብርና የመንፈስ ከፍታ ይሰማዋል፡፡ “አንበሳ ፤ ወንድ ነህ! በጣም ድንቅ ስራ ነው የሰራኸው…..ወዘተ” ሰዎች አድናቆትን ለመግለጽ የሚጠቀሙባቸው ቃላት ናቸው፡፡ አድናቆትን በተመለኩ ብዙ ምሁራን በጉዳዩ ላይ ተከራክረዋል የተለያዩ ጥናቶችንም አካሄደዋል፡፡ ምሁራኑ እንደ ርዕሰ ጉዳዮቻቸው ያገኙት ውጤትም ያንኑ ያህል ይለያያል፡፡ አንዳንዶች በጥናታቸው መሠረት አድናቆት ተስፍ ለቆረጡና ምንም ማድረግ አንችልም ብለው ለተቀመጡት እንደ ጉዞ ስንቅ በማገልገል እንደገና ተስፋቸውን አለምልመው ወደ ተሻለ ደረጃ እንዲደርሱ ይራዳቸዋል ሲሉ በተቃራኒው አድናቆት በተለይ የልጆችን መነሳሳት ይቀንሳል ፤ ጫናዎችን እንዳይቋቋሙ ያደርጋል ከፍ ሲልም ጥገኝነትን ይፈጥራል ይላሉ፡፡
የሂሁማኒሰቲክ ሳይኮሎጂ አቀንቃኞችም የልጆችን ባህሪ እየመረጥን ማድነቃችን ማንነታቸውን ሙሉ በሙሉ እንዳይቀበሉና እያደጉ ሲሄዱም ፤ መሆን በሚፈልጉትና (ideal self-concept) በሆኑት ማንነታቸው (real self-concept) መካከል ከፍተኛ ልዩነት ሊፈጠር ይችላል፡፡ ይህም ለስነ-ልቡና መታወክ አስተዋጽኦ ሊፈጥር ይችላል ይሉናል፡፡ ሂውማኒስቲኮቹ የሚያበረታቱት አንድን ሰው በሙሉ ከእነ እንከኑ መቀበልን ነው (unconditional positive regard)፡፡ ለነገሩማ ከወደዱ ከነ ንፍጡ ነው ይባል አይደል እንዴ በሀገራችን አባባል፡፡
አልፊ ኮን (2005)
አግባብነት ያለው ማበረታቻ እያገኘ ያደግ ልጅ በእራስ መተማመንን ይማራል
መቻቻል በሰፈነበት ሁኔታ ያደገ ልጅ ትዕግስተኝነትን ይማራል
ልጅ ከአድሎ ነጻ በሆነ ሁኔታ በአግባቡ ካደገ ፍትህን ይማራል
ልጅ ዋስትናና ደህንነት በተመላበት ኑሮ ካደገ ሰውን ማመንን ይማራል
ልጅን በማንነቱ ተቀብለን በማቅረብ ካሳደግነው ምሉዕ ፍቅር ከአለም ይማራል
ጥላቻ በተመላበት አካባቢ ያደገ ልጅ ጠባጫሪነትን ይማራል
ልጅ በሃፍረት ካደገ የጥፋተኝነት መንፈስን ይማራል
…. እንዳለው ዶርቲ ሎው
በየትኛውም ስፍራ የሚኖር የሰው ልጅ ህጻንም ይሁን አዋቂ አድናቆትንና ሙገሳን ይወዳል እንዲሁም ይፈልጋል፡፡ መደነቅ በሰዎች ዘንድ ትኩረት ማግኘታቸንን ስለሚያመላክት ተደናቂው ክብርና የመንፈስ ከፍታ ይሰማዋል፡፡ “አንበሳ ፤ ወንድ ነህ! በጣም ድንቅ ስራ ነው የሰራኸው…..ወዘተ” ሰዎች አድናቆትን ለመግለጽ የሚጠቀሙባቸው ቃላት ናቸው፡፡ አድናቆትን በተመለኩ ብዙ ምሁራን በጉዳዩ ላይ ተከራክረዋል የተለያዩ ጥናቶችንም አካሄደዋል፡፡ ምሁራኑ እንደ ርዕሰ ጉዳዮቻቸው ያገኙት ውጤትም ያንኑ ያህል ይለያያል፡፡ አንዳንዶች በጥናታቸው መሠረት አድናቆት ተስፍ ለቆረጡና ምንም ማድረግ አንችልም ብለው ለተቀመጡት እንደ ጉዞ ስንቅ በማገልገል እንደገና ተስፋቸውን አለምልመው ወደ ተሻለ ደረጃ እንዲደርሱ ይራዳቸዋል ሲሉ በተቃራኒው አድናቆት በተለይ የልጆችን መነሳሳት ይቀንሳል ፤ ጫናዎችን እንዳይቋቋሙ ያደርጋል ከፍ ሲልም ጥገኝነትን ይፈጥራል ይላሉ፡፡
የሂሁማኒሰቲክ ሳይኮሎጂ አቀንቃኞችም የልጆችን ባህሪ እየመረጥን ማድነቃችን ማንነታቸውን ሙሉ በሙሉ እንዳይቀበሉና እያደጉ ሲሄዱም ፤ መሆን በሚፈልጉትና (ideal self-concept) በሆኑት ማንነታቸው (real self-concept) መካከል ከፍተኛ ልዩነት ሊፈጠር ይችላል፡፡ ይህም ለስነ-ልቡና መታወክ አስተዋጽኦ ሊፈጥር ይችላል ይሉናል፡፡ ሂውማኒስቲኮቹ የሚያበረታቱት አንድን ሰው በሙሉ ከእነ እንከኑ መቀበልን ነው (unconditional positive regard)፡፡ ለነገሩማ ከወደዱ ከነ ንፍጡ ነው ይባል አይደል እንዴ በሀገራችን አባባል፡፡
አልፊ ኮን (2005)
በአንቶኒዮ ሙላ
No comments:
Post a Comment