Thursday, 12 April 2018








አድናቆት

ስለእራሱ ጥሩ ነገር እየተነገረው ያደገ ልጅ ማድነቅን ይማራል
አግባብነት ያለው ማበረታቻ እያገኘ ያደግ ልጅ በእራስ መተማመንን ይማራል
መቻቻል በሰፈነበት ሁኔታ ያደገ ልጅ ትዕግስተኝነትን ይማራል
ልጅ ከአድሎ ነጻ በሆነ ሁኔታ በአግባቡ ካደገ ፍትህን ይማራል
ልጅ ዋስትናና ደህንነት በተመላበት ኑሮ ካደገ ሰውን ማመንን ይማራል
ልጅን በማንነቱ ተቀብለን በማቅረብ ካሳደግነው ምሉዕ ፍቅር ከአለም ይማራል
ጥላቻ በተመላበት አካባቢ ያደገ ልጅ ጠባጫሪነትን ይማራል
ልጅ በሃፍረት ካደገ የጥፋተኝነት መንፈስን ይማራል
…. እንዳለው ዶርቲ ሎው
በየትኛውም ስፍራ የሚኖር የሰው ልጅ ህጻንም ይሁን አዋቂ አድናቆትንና ሙገሳን ይወዳል እንዲሁም ይፈልጋል፡፡ መደነቅ በሰዎች ዘንድ ትኩረት ማግኘታቸንን ስለሚያመላክት ተደናቂው ክብርና የመንፈስ ከፍታ ይሰማዋል፡፡ “አንበሳ ፤ ወንድ ነህ! በጣም ድንቅ ስራ ነው የሰራኸው…..ወዘተ” ሰዎች አድናቆትን ለመግለጽ የሚጠቀሙባቸው ቃላት ናቸው፡፡ አድናቆትን በተመለኩ ብዙ ምሁራን በጉዳዩ ላይ ተከራክረዋል የተለያዩ ጥናቶችንም አካሄደዋል፡፡ ምሁራኑ እንደ ርዕሰ ጉዳዮቻቸው ያገኙት ውጤትም ያንኑ ያህል ይለያያል፡፡ አንዳንዶች በጥናታቸው መሠረት አድናቆት ተስፍ ለቆረጡና ምንም ማድረግ አንችልም ብለው ለተቀመጡት እንደ ጉዞ ስንቅ በማገልገል እንደገና ተስፋቸውን አለምልመው ወደ ተሻለ ደረጃ እንዲደርሱ ይራዳቸዋል ሲሉ በተቃራኒው አድናቆት በተለይ የልጆችን መነሳሳት ይቀንሳል ፤ ጫናዎችን እንዳይቋቋሙ ያደርጋል ከፍ ሲልም ጥገኝነትን ይፈጥራል ይላሉ፡፡
የሂሁማኒሰቲክ ሳይኮሎጂ አቀንቃኞችም የልጆችን ባህሪ እየመረጥን ማድነቃችን ማንነታቸውን ሙሉ በሙሉ እንዳይቀበሉና እያደጉ ሲሄዱም ፤ መሆን በሚፈልጉትና (ideal self-concept) በሆኑት ማንነታቸው (real self-concept) መካከል ከፍተኛ ልዩነት ሊፈጠር ይችላል፡፡ ይህም ለስነ-ልቡና መታወክ አስተዋጽኦ ሊፈጥር ይችላል ይሉናል፡፡ ሂውማኒስቲኮቹ የሚያበረታቱት አንድን ሰው በሙሉ ከእነ እንከኑ መቀበልን ነው (unconditional positive regard)፡፡ ለነገሩማ ከወደዱ ከነ ንፍጡ ነው ይባል አይደል እንዴ በሀገራችን አባባል፡፡
አልፊ ኮን (2005)
በአንቶኒዮ ሙላ

No comments:

Post a Comment

"ምግብ የሚያስቸግሩ ልጆችን እንዴት እንመግባቸው" - ዶ/ር ንጉሤ ጫኔ ፤ የህፃናት ህክምና ስፔሻሊስት ሀኪም

ከአንድ እስከ ሦሥት ዓመት ያሉ ልጆች መደበኛ አመጋገብ የላቸውም። አንድ ቀን በድንብ ይበላሉ ሌላ ቀን ደግሞ ፈጽመው ምግብ መንካት አይፈልጉም። ቁርስ በደንብ በልተው ምሳ ላይፈልጉ ይችላሉ። ይህ የተለመደ ፀባያቸው ስለሆነ ...